BBC News, አማርኛ - ዜና

ዜና

ቢቢሲ አማርኛ በቲክቶክ

አስተማማኝ ዜና እና መረጃን ቅድሚያ ለማግኘት ቢቢሲ አማርኛን ቲክቶክ ላይ ይከተሉ

የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቪድዮዎች

የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቻናልን ይቀላቀሉ

አነጋጋሪ ጉዳይ

  • የምክክር ጉባኤ

    በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የክልል ፕሬዝደንቶች ሰጡ የተባለው አስተያየት እና የጎላው ልዩነት

    ወደ ማጠናቀቂያው በተቃረበው የአገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የአዲስ አበባ ጉዳይ መግባባት ያልተደረሰበት እና ሂደቱን ያዘገየ አጀንዳ ሆኗል። ሐሙስ ዕለት በተካሄደው ጉባኤ ላይ አዲስ አበባን በተመለከተ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ስለተነሱት ምክረ ሀሳቦች ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል። የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች አመራሮች መካከል በመዲናዋ ጉዳይ ልዩነት መታየቱንም ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።

  • ኢትዮጵያውያን በአሜሪካ

    ኢትዮጵያውያንን የሚመለከቱ አራት የፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢሚግሬሽን ውሳኔዎች

    ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት ዓመት ሊሞላው ወራት በቀረው የሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው፣ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ዒላማ ያደረጉ ትዕዛዞችን አሳልፈዋል። በተለያየ መንገድ ኢትዮጵያውያን ላይ ጫና ሊያሳድሩ የሚችሉ የትራምፕ አስተዳደር አራት ውሳኔዎችን እንመልከት።

  • 'ኤል ዳባ' የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ

    የግብፅ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ላይ ተገኝቷል የተባለው ጉድለት እና ያስነሳው ውዝግብ

    የግብፅ መንግሥት፣ በአገሪቱ የሚገነባው 'ኤል ዳባ' የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ማብላያዎች (ሪአክተር) ላይ "ጉድለት" እንደተገኘ በመግለፅ ግንባታውን የሚያከናውነው የሩሲያው ኩባንያ ላይ አቅርቦታል የተባለው ወቀሳ ውዝግብ አስነስቷል። “የኒውክሌር ደኅንነት አሠራር" ላይ ጥሰት ስለመፈጸሙ የወጣውን ዘገባ ተከትሎ ምላሽ የሰጡት የግብፅ ባለሥልጣናት፣ ጉዳዩን አስተባብለዋል።

  • የአገራዊ ምክክር አርማ

    አዲስ አበባ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫነቷ በሕገ መንግሥት እንዲደነገግ" ምክረ ሀሳብ ቀረበ

    በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ጉባኤ ሲከራክር በቆየው የአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የከተማዋ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫነት በፌደራል ሕግ መንግሥት እንዲሰፍር" የሚጠይቅ ምክረ ሃሳብ መቅረቡን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ። ከተማዋ "ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚኖራትን ግንኙነት" በተመለከተ ግን ኮሚሽኑ የመጨረሻውን የሚለው ምክረ ሀሳብ ለመንግሥት እንደሚያቀርብ ማስታወቁን አንድ ምንጭ ገልጸዋል።

  • ድሬዳዋ

    በድሬዳዋ ከተማ ጉዳይ ላይ በሀገራዊ ምክክሩ ከምን ስምምነት ላይ ተደረሰ?

    በሀገራዊው ምክክር ላይ የድሬዳዋ ከተማ በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ ስር ምክክር ከተደረገባቸው ሁለት ከተሞች አንዱ ነው። ከኦሮሚያ እና ከሶማሌ ክልሎች በተወከሉ የምክክሩ አባላት መካከል ከፍተኛ የይገባኛል ክርክር እንደተደረገባት በምክክሩ ላይ የተሳተፉ ታማኝ ምንጭ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ ሰፊ መነጋገሪያ መሆኑ፣ የድሬዳዋ ጉዳይ ብዙም ትኩረት እንዳያገኝ አድርጎታል። ለመሆኑ በድሬዳዋ ላይ ምን ዓይነት ስምምነት ተደረሰ?

  • የአዲስ አበባ ገጽታ በከፊል

    የአዲስ አበባን ጉዳይ ቅርቃር ውስጥ ያስገባው "ከበላይ የመጣ" ሃሳብ እና የምክክር ኮሚሽኑ ምላሽ

    አንድ ወር ባስቆጠረው አገራዊ ምክክር ስምንት አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ የቆዩት ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ወደ መቋጫው እየተቃረቡ ነው። በዚህ ሂደት የአዲስ አበባ ጉዳይ ከሌሎች አጀንዳዎች በበለጠ አነጋጋሪ እና ስምምነት ላይ ለመድረስ አዳጋች ሆኖ ታይቷል። በአዲስ አበባ የምክክር አጀንዳ ላይ የተከሰተው ምንድን ነው? ያላግባቡት ጉዳዮችስ የትኞቹ ናቸው?

  • ለሽምግልና የተዘጋጁ ግዙፍ የአበባ እቅፎች

    እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር የሚወጣባቸው ግዙፍ የሽምግልና አበባዎች፡ የአበባ አብዮት ወይስ የባህል ለውጥ?

    ከጋብቻ በፊት የሚደረገው የሽምግልና ሥነ ሥርዓት ከፍተኛ ድግስ እና ገንዘብ የሚፈስበት እየሆነ መጥቷል። ከሚዘጋጀው ድል ያለ ድግስ ባሻገር በመቶ ሺዎች ብር የሚያስወጡ ቄንጠኛ ግዙፍ የአበባ ‘እቅፎች’ ደግሞ የሽምግልናው ሥርዓት አካል ሆነዋል። በተለይ የሚቀርበው የአበባ ስጦታ መነጋገሪያ ሆኗል። የሽምግልና ሥነ ሥርዓት የሰርግን ቦታ እየተካ ነው? ግዙፉ የአበባ ስጦታስ ከየት የመጣ ልማድ ነው?

  • የአብን ሊቀ መንበር ዶ/ር በለጠ ሞላ

    አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ "መዋቅራዊ ጥሰቶች" እና "አንድ ወገን ብቻውን የሚወስንበት እንቅስቃሴ" ታይቷል ሲል ከሰሰ

    የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፣ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ "ከተራ የአሠራር ግድፈት" የዘለሉ "ተደጋጋሚ እና የተደራጁ ጥፋቶች ተፈጽመዋል" ሲል ከሰሰ። "ገዢው አካል መዋቅራዊ ጥሰቶችን" እንደፈጸመ በማንሳት የከሰሰው አብን፣ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ "የከተማዋ ነዋሪዎች ድምፅ እና ፍላጎት በአግባቡ ሳይወከል" መታለፉን ገልጿል። በሂደቱ ላይ የተፈጸሙት "ተደጋጋሚ እና የተደራጁ ጥፋቶች" የሀገራዊ ምክክሩን "ተዓማኒነት፣ አካታችነት፣ ገለልተኝነት እና ፍትሐዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚስገቡ" እንደሆኑም ገልጿል።

  • ከተከሳሾቹ መካከል አቶ ዮሐንስ፣ መስከረም፣ ጎበዜ፣ ክርስቲያን እና ሲሳይ

    ከአማራ ክልል ቀውስ ጋር በተገናኘ በሽብር ለተከሰሱት የቀረበው የይቅርታ ሰነድ ምን አካቷል? ተከሳሾቹስ ምን ምላሽ ሰጡ?

    በአማራ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ በሽብር ለተከሰሱት ከሦስት መቶ በላይ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ግለሰቦች በይቅርታ እንዲለቀቁ ሂደት ላይ ይገኛሉ። ለሽብር ተከሳሾች የቀረበው የይቅርታ ሰነድ በክልሉ ለተፈፀሙ ግድያዎች እና ጉዳቶች ተከሳሾቹ ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚጠይቅ መሆኑን ቢቢሲ የተመለከተው ሰነድ ያሳያል።

  • የመተከል ዞን ዋና ከተማ ግልገል በለስ

    በመተከል ዞን ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ

    በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ጥቃቱ የተፈፀመው ማክሰኞ ነሐሴ 6/ 2018 ዓ. ም. ጠዋት 12 ሰዓት ላይ በዞኑ ዋና ከተማ ግልገል በለስ በሚገኙ ቤተ ክርስቲያናት እና መናኸሪያ ላይ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

  • የመንግሥት እና የፋኖ ተፋላሚ ኃይሎችን እንዲሁም የሰላማዊ ሰዎችን ስቃይ የሚያሳይ ምሥል

    በተስፋ ማጣት እና በሞት መሀል፡ የአማራ ክልል ሦስት የጦርነት ዓመታት

    በአማራ ክልል ላለፉት ሦስት ዓመታት በፋኖ ኃይሎች እና በመንግሥት መካከል የሚካሄደው ግጭት የበርካቶችን ሕይወት ቀጥፏል፤ ከፍተኛ ሰብኣዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ውድመትም አድርሷል። ቢቢሲ አማርኛ ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች ከፍርድ ውጭ ግድያዎችን ጨምሮ ንጹኃን እስር እና እንግልትን እያስተናገዱ መሆኑን ይናገራሉ። የትጥቅ ግጭቶችን የሚመዘግበው አክሌድ ከጥር እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜውስት ብቻ ከስምንት ሚሊዮን በላይ ሰዎች 'ለግጭት' ተጋልጠዋል ብሏል። ቢቢሲ በግጭቱ በቀጥታ የተጎዱ ነዋሪዎችን እንዲሁም ባለሙያዎችን አነጋግሮ ቀጣዩን ዘገባ አሰናድቷል።

  • ዮናስ መኳንንት

    "አዲስ አበባ እንደ እንግዳ ካልሆነ ከዚህ በኋላ ለመኖር የምመጣ አይመስለኝም"

    የሥዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያ የሆነው ዮናስ መኳንንት፤ ተወልዶ ያደገባትን፣ የእንጀራ ገመዱ የነበረችውን አዲስ አበባን ጥሎ ገጠር ከገባ ከጥቂት ወራት በኋላ ሁለት ዓመት ይሞላዋል። "እኔ እዚህ ከመጣሁ ትልቅ እረፍት ነው የሚሰማኝ። በጣም ሰላማዊ ቦታ ነው፤ ምንም ዓይነት የመኪና ድምጽ የለም፣ የምትሰማው የእንስሳት ድምጽ ብቻ ነው" ይላል።

ቢቢሲ አማርኛን በዋትስአፕ ላይ ያግኙ

የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት

የኢንተርኔት ዳታን በመቆጠብ የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽን በቀላሉ ማንበብ ይፈልጋሉ?

የቢቢሲ አማርኛን ድረ ገጽ በቀላሉ በመክፈት ዜና እና ታሪኮችን በጽሑፍ ብቻ ያንብቡ!

ከየፈርጁ

አጃኢብ!

የተመለሱ ጥያቄዎች

ሌላ ዕይታ

በስፋት የተነበቡ